a
በምህንድስና፣በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ በጥናት፣ዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ደረጃ በጥራት እና በብቃት ተወዳዳሪና ተመራጭ ኩባንያ እ.ኤ.አ.በ2030 ተፈጥሮ ማየት፡፡ በብቁ ባለሙያዎች ጥራት ያለው፣ በፈጠራ ላይ የተመሰረተና ቀልጣፋ የምህንድስና አገልግሎት በታማኝነት የመስጠት መርህን አንግቦ በ 2008 ዓ.ም የተመሰረተው ላሊበላ የጥናት፣ዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች ሌላኛው የጋፋት ኢንዶውመንት ኩባንያ ነው፡፡ ኩባንያው በውሃ፣በመንገድና ህንጻ ስራዎች ዘርፍ የጥናት፣ዲዛይንና ሱፐርቪዥን አገልግሎት፤በንግድና ኢንቨስትመንት የጥናትና የማማከር እንዲሁም የአከባቢ ተጽእኖ ግምገማና ጥናት አገልግሎቶችን ይሰጣል፡፡